📢 ማስታወቂያ
በፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለመማር ተመዝግባችሁ ፈተና በመጠባበቅ ላይ ላላችሁ ተማሪዎች በሙሉ፤
ትምህርት ሚኒስቴር ለ2019 የትምህርት ዘመን ትምህርት በሚሰጥባቸው ነባርና አዲስ የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በ9ኛ እና 10ኛ ክፍል ተማሪዎችን አወዳድሮ ለመቀበል ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት ተመዝግባችሁ በመጠባበቅ ላይ ያላችሁ ተማሪዎች የፈተና ፕሮግራም መውጣቱ ይታወሳል።
ይሁን እንጂ አንዳንድ ተማሪዎች የመፈተኛ ቦታቸውን ባለማዎቃቸው በአንድ ቀን ማራዘም አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል።
ስለሆነም ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም የሙከራ ፈተና እንዲሁም ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም ለዋናው ፈተና ፕሮግራም የወጣ መሆኑን አውቃችሁ በዚህ ፕሮግራም መሰረት ከጠዋቱ 2:30 በተመደባችሁባቸው ጣቢያዎች ራሳችሁን የሚገልጽ መታወቂያ በመያዝ እንድትፈተኑ እንገልጻለን።
September 1, 2026 21.1K 415