ፖለቲከኛ ልደቱ አያሌው የሙዚቃ አልበም ሊለቁ ነው!
ላለፉት ሶስት አስርት አመታት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ጉልህ እንቅስቃሴ በማድረግ የሚታወቁት አቶ ልደቱ፤ ሀሳብን በዜማ በሚል ለአዲስ አመት የሙዚቃ አልበም ሊያሰራጩ መሆኑን ገልጸዋል።
ፖለቲከኛው አዲስ የከፈቱትን የዩቲዩብ ገጽ ይፋ ባደረጉበት ወቅት እንዳሳወቁት የሙዚቃ አልበሙን ያዘጋጁት አርቴፊሻል ኢንተለጀንስን በመጠቀም ነው።
እንደሚታወሰው ቴዲ አፍሮ ኢቶሪካ አልበሙን ካሰራጨ በኋላ የፈጠረውን ተጽእኖ ተከትሎ አቶ ልደቱ በወቅቱ፣ "የመንፈስ ቅናት አደረብኝ" ሲሉ ገልጸው ነበር።

9
5
4September 6, 2026 2.8K