የግጥም ጥግ: post #641 — TG.ME

:
አቅጄ ነበረ በልኬ ሰፍቼ
‎አጣማጅ አቻዬን ከ'ቅዴ ከትቼ
‎በውጣ ውረዴ በጎንበስ ቀናዬ
‎ነገን እያሳየሽ የቆምሽ ከኋላዬ
‎ነብስሽ እና ነብሴ አንዳች ሳይሞክሩ
‎እንደተላመዱ ምነው ቢፋቀሩ
‎ቀናት ሲጋልቡ  ፣ አዝማናት ሲረግቡ
‎ጣፋጭ ቃሎቻችን ከጎታ ሳይገቡ
‎ልጆቻችን አድገው በወግ ሳያገቡ
‎ይሄን ሁሉ ሳላይ ፍፃሜ ትንቢቱን
‎ባንኜ ሳልነቃው የህልም ዓለም 'ሌቱን
‎እንዳላጣሽ ፈራሁ ያይኖቼን ማረፊያ
‎ወይ አላሳስርሽ እን ስርቆት ዝርፊያ
‎አልተክልሽም ነገር እንደ ደጅ አበቦች
‎ይዤሽ አልዞር ብትሆኝ እንደ ደሜ ስሮች
‎እና ምን ተሻለ፥
‎እንደው እንደ ዘበት እንደ አፍ ወለምታ
‎ሳይጨነቁበት እንዳስተጋቡት ቃል እንደ ቀን እፎይታ
‎ምነው ቢታከሙት አንቺጋራ መንተው የልብን ትርታ
‎እውነትን ተናገርሁ አምነሽ ተቀበይኝ
‎እኔ መሽቶብኛል አንቺም አሳድሪኝ።

✍️ Zemed
@ getmtg
@getmtg
❤8👏2🔥1
May 19, 2026 731 1 2