ወላጆች ሆይ!
የልጅ አስተዳደግ መሠረታችሁ በእናንተና በልጃችሁ መካከል ፍቅርና የጋራ መተሳሰብ ላይ የተመረኮዘ ይሁን፤ በማስፈራራትና በማስጨነቅ ላይ የተመሠረተ አይሁን፤ ምክንያቱም እነዚህ ሁለቱ ዘላቂ አይደሉምና ነው።
ልጆቻችሁን በጉልበታችሁ የምትቆጣጠሩት ከሆነ፣ እናንተ እንደምትደክሙ እነርሱ ደግሞ አድገው እንደሚጠነክሩ አስታውሱ፤ ያኔ በእናንተና በእነርሱ መካከል ፍቅር ከጠፋ እንዴት ትቆጣጠሩታላችሁ?
ፍቅር ፍቅርን ይወልዳል፤ ልጅም ከተቀበለው ይገነዘበዋል፣ ለሰጠውም በተመሳሳይ ይመልሳል። ፍቅርን ከተቀበለ በምላሹ ሌሎችን እንደሚወድ ሆኖ ያድጋል፤ ጭካኔንና ግዴለሽነትን ከተቀበለ ግን ጠበኛና ጨካኝ ሆኖ ያድጋል።
እያስተዋልን!
#የሂዳያ_ትውልድ #ለወላጆች #ምክር_ለተርቢያ
📮 የመጪው ትውልድ ሃላፊነት የጋራችን ነው! መልዕክቱን ሼር በማድረግ ለብዙዎች እናድርስ!
💫 https://t.me/HidayaTerbiya 💫
Forwarded fromHidaya Terbiya II ሂዳያ ተርቢያ
Telegram
Hidaya Terbiya II ሂዳያ ተርቢያ
Hidaya Terbiya
ሂዳያ ተርቢያ
የመልካም ትውልድ ማፍርያ!
@HidayaTerbiya

June 4, 2025 172 1