የዓለም የልደት ምጣኔ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ከሚያስፈልገው ዝቅተኛ ደረጃ በታች ወደቀ
በዓለም ታሪክ በጦርነትም ሆነ በወረርሽኝ ወቅት አጋጥሞ የማያውቅ የልደት ምጣኔ ቅናሽ መመዝገቡን የ ZME Science ጥናት ይፋ አደረገ።
የሕዝብ ቁጥርን ሳይቀንስ በተረጋጋ ሁኔታ ለማስቀጠል በአማካይ ለአንዲት ሴት 2.1 – 2.2 ልጅ መውለድ የሚያስፈልግ ቢሆንም፣ አሁን ያለው መረጃ ግን ከዚያ በእጅጉ የወረደ ነው።
እንደ አዲሱ መረጃ፣ በታይዋን 0.69፣ በደቡብ ኮሪያ 0.8፣ በሲንጋፖር 0.87 እና በቻይና 0.93 ልጅ ብቻ ይወለዳል።
በሩሲያም የልደት ምጣኔው 1.4 አካባቢ ይገኛል።
በዚሁ ሁኔታ ከቀጠለ የዓለም ሕዝብ ቁጥር በ 2056 ዓ.ም (እ.ኤ.አ) 9 ቢሊዮን አካባቢ ደርሶ ከፍተኛው ቦታ ላይ ይደርሳል ተብሏል።
ከዚያ በኋላ ግን ዓለም አቀፍ የሰራተኛ እጥረት የሚያጋጥም ሲሆን፣ በጡረታ እና በጤና ስርአቶች ላይ ደግሞ የገንዘብና የግብአት ጫና ከፍተኛ ይሆናል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter

5
3
2August 26, 2026 3.1K 5