ከህይወት ገፅ የግጥም መድብል: post #411 — TG.ME

በእውቀቱ_ስዩም
አገሬ

አገርን ለፈሪ፥ አይሰጡም አደራ
ዳር አድርጎት ያድራል፥ የማሀሉን ስፍራ፤

አገርን ለፈሪ፥ አደራ ብሰጠው
የዘላለም ቤቴን፥ ባንድ አዳር ለወጠው፤

አባ ነጋ ሞቶ

አባ ጽልመት መጥቶ

አገሬ እንደ ዛጎል፥ እያብረቀረቀች
ከባሕር ተገፍታ፥ የብስ ላይ ወደቀች።
❤14
June 25, 2026 1.3K 3