አል ነስር በሮናልዶ ግብ አሸንፏል::
በሳውዲ ፕሮ ሊግ አል ነስር ከአል ታዎን ጋር ያደረገውን ጨዋታ 2ለ1 በሆነ ውጤት ማሸነፍ የቻለ ሲሆን ሳሙ እና ክርስቲያኖ ሮናልዶ ነስርን አሸናፊ ያደረጉ ግቦችን አስቆጥረዋል::
የማሸነፊያዋን ግብ ያስቆጠረው ክርስቲያኖ ሮናልዶ በእግር ኳስ ህይወቱ ያስቆጠራቸውን ጎሎች 978 ማድረስ ችሏል::
ውጤቱን ተከትሎ አል ነስር ከ4 ጨዋታዎች 12 ነጥቦችን በመሰብሰብ ሊጉን እየመራ ይገኛል::

August 28, 2026 82