መኪና ተፈብርኮ ዘግይቶም ቢሆን በአባቶቻችን ኢትዮጵያ ሲገባ መቅደም ቢያቅተን እንኳ መኮረጅ ትተን የሰይጣን… — Hasen Injamo — TG.ME

-> መኪና ተፈብርኮ ዘግይቶም ቢሆን በአባቶቻችን ኢትዮጵያ ሲገባ መቅደም ቢያቅተን እንኳ መኮረጅ ትተን የሰይጣን ሥራ ወደማለት ሄድን:: የጋሪ መዘውር እንኳ መሥራት ሳንችል የኤሌክትሪክ መኪና መጣብን::

-> በእኛው ዘመን ሞባይል ተመርቶ ኢትዮጵያ ሲገባ ማምረት ትተን ትላልቅ ቀረጥ, ኮንት^ሮባንድ ጋር መሯሯጥ እና ስክሪን ሴቨር የሚሆን ፎቶ ላይ አተኮርን::

-> በልጆቻችን ዘመን Ai ሲመጣ ምርትን ማቀላጠፍ ትተን የማምረቻ ቦታዎችን የው^ጊያ ምሽግ, የሰው መኖሪያና መሥሪያ ቦታዎችን ፓርክ አድርገናቸዋል:: ገና ከጫካ የሚመጣ ቡድን ያሻሽለናል ብለን እንጠብቃለን::
_
ወቀሳ ብቻ ሆነ እንዴ?
ይሁና!
❤31😢8✍2👏2🙈1
September 6, 2026 1.7K