አዲስ ሪፖርተር - NEWS: post #30880 — TG.ME

"ከቡርኪና ፋሶ ውጡ ካልሆ ትሞታላችሁ‼️

የቡርኪና ፋሶው መሪ ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ ከሽብርተኞች ጋር ድርድር አላደርግም አሉ።

የቡርኪና ፋሶ መሪ ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ አገራቸውን እያተራመሱ ካሉ ታጣቂ እና አሸባሪ ቡድኖች ጋር ምንም ዓይነት ድርድር አናደርግም ብለዋል።

ከቡድኖቹ ጋር ምንም ዓይነት ድርድር የማድረግ ፍላጎት እንደሌላቸውና የማያወላውል ጠንካራ አቋም መያዛቸውን ይፋ አድርገዋል።

ካፒቴን ትራውሬ ለታጣቂ ቡድኖቹ ግልጽና ወሳኝ የሆነ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ከቡርኪና ፋሶ ውጡ ካልሆነ ትሞታላችሁ ብለዋል።

መንግስት የአገሪቱን አንድ ስንዝር መሬት እንኳ ለሽብርተኞች አሳልፎ እንደማይሰጥና ሀገሪቷ ሉአላዊነቷ እስኪረጋገጥ ድረስ ውጊያው እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።

የሀገሪቱ ሰላም የሚረጋገጠው በድርድር ሳይሆን በመከላከያ ሰራዊት ጥንካሬ ነው ሲሉ ጠንካራ አቋማቸውን ገልጸዋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤36👍21🤣3🥰1🤔1💔1👀1