ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ‼ በደሴ ከተማ በተደጋጋሚ የመብራት ትራንስፎርመሮችንና የቴሌ መሠረተ ልማቶችን… — Wasu Mohammed - ዋሱ መሀመድ — TG.ME

ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

በደሴ ከተማ በተደጋጋሚ የመብራት ትራንስፎርመሮችንና የቴሌ መሠረተ ልማቶችን ሲዘርፉ የነበሩ ወንጀለኞች በሚሊዮን የሚቆጠር ንብረትና ከግብረ-አበሮቻቸው ጋር በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የደሴ ከተማ ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።

​በጉዳዩ ላይ የኃላፊዎች አስተያየት፦
📌​ኮማንደር ሠይድ አሊ (የደሴ ከተማ ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ)፦ ዘራፊዎቹ መያዛቸው ትልቅ ስኬትና ህግን ማስከበር ማሳያ መሆኑን ገልጸው፣ ህዝቡ ከፀጥታ ኃይሉ ጋር ያለው ትብብር እንዲጠናከር ጥሪ አቅርበዋል።

📌​ኮማንደር ጥላሁን ታደሰ (የደሴ ከተማ ፖሊስ መምሪያ አዛዥ)፦ ድርጊቱ ልማትን ለማደናቀፍ የተደረገ እኩይ ተግባር መሆኑን ጠቅሰው፣ በልዩ ቡድን በተደረገ ምርመራ ውጤቱ እንደተገኘና ተጠርጣሪዎች ላይ ምርመራው እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

📌​አቶ ሀብቱ አበበ (የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የደሴ ሪጅን ዳይሬክተር)፦ ከሐምሌ ወር ጀምሮ ይፈጸም የነበረውን ስርቆትና የንብረት ውድመት ለማስቆም ለተደረገው ከፍተኛ ትብብር ምስጋና አቅርበዋል።

📌​ኮሎኔል ገዛህኝ አለባቸው (የሰሜን ምስራቅ ሪጅን ሴኩሪቲ ማናጀር)፦ ተቋማቸው ጉዳዩን ከአጋር የፀጥታ ኃይሎች ጋር በመቀናጀት በትኩረት እየሰራበት እንደሚገኝ አስታውቀዋል።
(መረጃው የደሴ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ህ/ግ ነው)
#WasuMohammed
👇እዚህ ድምፅ ይስጡ👇
https://yekinlibochaward.org/nominees/wasu-mohammed
====================
ወቅታዊ እና የታመኑ መረጃዎች እንዲደርሱዎ  የቴሌግራም ቻናሉን join በማድረግ በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
❤127👍33👌8🙈8🥰2🙏2🕊2👏1🤝1
September 5, 2026 22.8K 22