አባይ ቴሌቪዥን ማስጠንቀቂያ ተሰጠው! "የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን በአባይ ቴሌቪዥን ላይ ጠንከር… — Sheger Press️️ — TG.ME

አባይ ቴሌቪዥን ማስጠንቀቂያ ተሰጠው!

"የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን በአባይ ቴሌቪዥን ላይ ጠንከር ያለ ማስጠንቀቂያ ሰጠ።

ባለስልጣኑ ባለፉት ሦስት ወራት ባደረገው ክትትል፣ ጣቢያው በዜናዎቹና በፕሮግራሞቹ ላይ ከባድ የሕግና የሙያ ስነ-ምግባር ጥሰቶችን ፈጽሟል ብሏል።

ከጥሰቶቹ መካከል፦ከባህላችን ያፈነገጡ ፀያፍ ንግግሮችን ማሰራጨት፣የሴቶችን ክብር የሚነኩ ይዘቶች፣እና ያልተረጋገጡ የዜና ምንጮችን መጠቀም ይጠቀሳሉ።

የጣቢያው ኃላፊዎች ጥፋቱን አምነው ይቅርታ የጠየቁ ሲሆን፣ በአፋጣኝ እርምጃ እንደሚወስዱም ቃል ገብተዋል።
👎18❤7
September 1, 2026 3.5K 2 5