አባይ ቴሌቪዥን ማስጠንቀቂያ ተሰጠው!
"የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን በአባይ ቴሌቪዥን ላይ ጠንከር ያለ ማስጠንቀቂያ ሰጠ።
ባለስልጣኑ ባለፉት ሦስት ወራት ባደረገው ክትትል፣ ጣቢያው በዜናዎቹና በፕሮግራሞቹ ላይ ከባድ የሕግና የሙያ ስነ-ምግባር ጥሰቶችን ፈጽሟል ብሏል።
ከጥሰቶቹ መካከል፦ከባህላችን ያፈነገጡ ፀያፍ ንግግሮችን ማሰራጨት፣የሴቶችን ክብር የሚነኩ ይዘቶች፣እና ያልተረጋገጡ የዜና ምንጮችን መጠቀም ይጠቀሳሉ።
የጣቢያው ኃላፊዎች ጥፋቱን አምነው ይቅርታ የጠየቁ ሲሆን፣ በአፋጣኝ እርምጃ እንደሚወስዱም ቃል ገብተዋል።
18
7September 1, 2026 3.5K 2 5


