ፍልሰታ ጾም ( ሱባኤ) 📝""አቤቱ የሆነብንን አስብ ተመልከት"" ሰቆቃ ኤር. ፭፥፩ ♣ በሀገራችን ኢትዮጵያ… — ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ ( Ethio Beteseb Media) — TG.ME

📌ፍልሰታ ጾም ( ሱባኤ)

📝""አቤቱ የሆነብንን አስብ ተመልከት""
                ሰቆቃ ኤር. ፭፥፩

በሀገራችን ኢትዮጵያ መቼም በማይረሳ የሀዘን ሰቆቃ ፦ ካህናት ሲገደሉ፤ አብያተክርስቲያን ሲቃጠሉ ፤ ወገኔ እየተገደለ ሀብት ንብረቱ ሲዘርፍ አምላክ ሆይ የሆነብንን አስብ በማለት በዚህ ሱባኤ እንዲህ ብለን እንማፀን ኃይላችን እሱ ነውና ፦፦፦፦

"ልባችንን ከእጃችን ጋር በሰማይ ወዳለው ወደ እግዚአብሔር እናንሣ።"
(ሰቆቃው ኤርምያስ ፫: ፵፩) እግዚኦ ማሀረነ እንበል ፦፦

" እግዚአብሔር ከሰማይ እስኪጐበኝና እስኪመለከት ድረስ ዓይኔ ሳታቋርጥ ዝም ሳትል እንባ ታፈስሳለች።"
(ሰቆቃው ኤርምያስ ፫: ፵፱-፶) እንዳለ ነብዩ በእንባ እንማፀን ወደ ጌታ፦፦

" ስለ ምን ለዘላለም ትረሳናለህ? ስለ ምንስ ለረጅም ዘመን ትተወናለህ?"
(ሰቆቃው ኤርምያስ ፭:፳) መከራውን ከእኛ እንዲያርቅ እንለምን ፦፦

" አምላካችን ሆይ፥ አንተ አትፈርድባቸውምን? ይህን የመጣብንን ታላቅ ወገን እንቃወም ዘንድ አንችልም፤ የምናደርገውንም አናውቅም፤ ነገር ግን ዓይኖቻችን ወደ አንተ ናቸው።"
(መጽሐፈ ዜና መዋዕል ካልዕ ፳፡ ፲፪)
በማለት ፍርዱን ለፈጣሪ እንስጥ፦፦

" አቤቱ፥ ማረን አንተን ተማምነናል፤ ጠዋት ጠዋት ክንድ በመከራም ጊዜ ማዳን ሁነን።"
(ትንቢተ ኢሳይያስ ፴፫: ፪) መታመኛችን እሱ ነውና ዘወትር የምህረት ክንዱን እንዲዘረጋልን ማረን እንበል ፦፦

" ማረን አቤቱ ማረን"
(መዝሙረ ዳዊት ፼፳፫: ፫) ዛሬ ዐይናችን ያየነውን ፣ ጃሮአችን የሰማውን የመረረ ሀዘንና መከራ ከእኛ እንዲያርቅ በሱባኤው ማረን አቤቱ ማረን እንበል ፤ የሞቱትን ነፍስ ይማር ፤ የተጎዱትን ጨርሶ ምህረቱን ይላክልን ፣ ለሕዝቡ መጽናናትን ያድልልን፤ ቤተክርስቲያችንን ከክፉ ይጠብቀልን ፤ ሀገራችንን ኢትዮጵያንን ሰላም ያድርግልን፤ ለዘመናት ተዋዶና ተከባብሮ የኖረውን ክርስቲያኑና ሙስሊሙን ለመለያየት እሳት የሚያፍሙትን ልቦና ይስጥልን!!!!  ሱባኤውን በሰላም አስጀምሮ እንዲያስጨርሰን የእርሱ መልካም ፈቃድ ይሁን!!!!
      
        
👉የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በረከት እና ረድኤት በሁላችን ይደርብን ፦ መልካም ሱባዔ🙏


     📍ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ
❤97🥰5👍3👎1
August 6, 2026 6K 19 12