እንድታውቁት የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት የውክልና አገልግሎቱን በአምስት ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች… — አለ ሕግ — TG.ME

#እንድታውቁት

የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት የውክልና አገልግሎቱን በአምስት ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ከወረቀት ነጻ በሆነ ሲስተም ተደራሽ ማድረግ መጀመሩን አሳውቋል።

ሜክሲኮ በሚገኘው ቅርንጫፍ አስር ልዩ እና መደበኛው ቅርንጫፍ ፣አያት አደባባይ ሎሚያድ ሱፐርማርኬት በሚገኘው ቅርንጫፍ አስራአንድ  እንዲሁም ካዛንቺስ እናት ታወር ላይ በሚገኘው  ቅርንጫፍ ስምንት እና ቦሌ በሚገኘው ቅርንጫፍ አስራሁለት ጽ/ቤቶች ነው  አገልግሎቱን መስጠት የተጀመረው።

በቅርቡም በሁሉም ቅርጫፎች ተግባራዊ  ለማድረግ እየሰራሁ እገኛለሁ ሲል የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት አስታውቋል።

ከተገልጋዮች  ምን ይጠበቃል ?

⚫https://dars.gov.et:5102 ሊንክ በመጫን መግባት፤

⚫ ብሄራዊ መታወቂያን በመጠቀም አስፈላጊ ዶክመንቶችን መጫን

⚫ ወደተጠቀሱት ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ማቅናት

⚫ የተጫነውን መረጃ መያዝ የሚያስፈልግ ሲሆን ዶክመንቱ ተመሳክሮ ትክክለኛነቱ  ሲረጋገጥ የኤሌክትሮኒክ ፊርማ  (signature  pad) በመፈረም የውክልና ሰነዱ በኦንላየን ይላካል።

⚫ በሰነዱ መገልገል ሲፈልጉ የሰነዱን ትክክለኛነት በQR Code ማረጋገጥ ይችላሉ።

የሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት ከወረቀትአልባ አገልግሎት በተጨማሪ በቴሌሳይን  መተግበሪያ አማካይነት የቤተሰብ የጠበቃ እና የአስተዳደር ውክልና አገልግሎት ወደተቋም መምጣት ሳይጠበቅባቸው ካሉበት ሆነው ማግኘት የሚያስችላቸው አሰራር መተግበሩን አስታውሷል።

@TikvahethMagazine
❤16👍8
August 16, 2026 4.6K 37