በባህር ዳር ሰዎችን በማገት የተሳተፉ አምስት ተጠርጣሪዎች ተያዙ‼ ​ በባህር ዳር ከተማ ሶስት ነጋዴዎችን… — Wasu Mohammed - ዋሱ መሀመድ — TG.ME

በባህር ዳር ሰዎችን በማገት የተሳተፉ አምስት ተጠርጣሪዎች ተያዙ

​ በባህር ዳር ከተማ ሶስት ነጋዴዎችን አፍነው በመውሰድ ለ11 ቀናት አግተው ያቆዩ እና 3 ሚሊዮን 370 ሺህ ብር የተቀበሉ አምስት የወንጀል ቡድን አባላት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የከተማዋ ፖሊስ አስታወቀ።

​በቁጥጥር ስር ከዋሉት ተጠርጣሪዎች መካከል ወንጀሉን የመራው በቀበሌ 06 የኤሌክትሮኒክስ ሱቅ ባለቤት አብርሃም ጫኔ፣ ለእገታው የኮድ 04-04343 ቶዮታ ሂሉክስ የመንግስት ተሽከርካሪ ያዋለው አሽከርካሪ መለሰ፣ ታጋቾቹን በ170 ሺህ ብር ክፍያ ደብቆ ያቆየ የህንፃ አስተዳዳሪ እንዲሁም በገንዘብ ዝውውሩ የተሳተፉት አበበ ጌቴ እና ከአዲስ አበባ የተሳተፈ ተባባሪ ይገኙበታል።

​ከነተሽከርካሪው በተጨማሪ አንድ ማካሮቭ እና አንድ ክላሽንኮቭ የጦር መሳሪያዎች መያዛቸውን የገለጸው ፖሊስ፤ የመንግስት ተቋማት በተሽከርካሪዎቻቸው ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እንዲያደርጉ አሳስቦ ቀሪ ተጠርጣሪዎችን የመያዝ ስራ መቀጠሉን አስታውቋል።(አማራ ፖሊስ)
#WasuMohammed
👇እዚህ ድምፅ ይስጡ👇
https://yekinlibochaward.org/nominees/wasu-mohammed
====================
ወቅታዊ እና የታመኑ መረጃዎች እንዲደርሱዎ  የቴሌግራም ቻናሉን join በማድረግ በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
❤83👏21✍8👍8🥰4👌3🕊2🤝1
September 4, 2026 16K 27