ለጤና ባለሙያዎች የተሰጠ ምላሽ‼
የአማራ ክልል የጤና ዘርፍ የትርፍ ሰዓት ሥራ ክፍያ መመሪያ (ቁጥር 68/2018) ማጠቃለያ
የ24/7 የህክምና አገልግሎትን ሳያቋርጡ ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎት ለመስጠት የወጣው አዲሱ መመሪያ ዋና ዋና ነጥቦች፦
💰 1. የትርፍ ሰዓት አከፋፈል ስሌት (ከሥራ ግብር ነፃ)፦
• የሥራ ቀናት (ምሽት 12፡00 - 4፡00)፦ የመደበኛ ሰዓት × 1.25
• የሥራ ቀናት (ምሽት 4፡00 - ንጋት 12፡00)፦ የመደበኛ ሰዓት × 1.5
• ቅዳሜና እሁድ (የእረፍት ቀናት)፦ የመደበኛ ሰዓት × 2.0
• የሕዝብ በዓላት ቀናት፦ የመደበኛ ሰዓት × 2.5
• ተጠባባቂ (On-call)፦ ካልተጠሩ 30% | ተጠርተው ከሰሩ 100%
⚠️ 2. ዋና ዋና የአሰራርና የዲሲፕሊን ሕጎች፦
• በወር ከ212 ሰዓት በላይ መስራት አይቻልም (ልዩ ሁኔታዎች ካልተፈቀዱ በስተቀር)።
• የትርፍ ሰዓት ሰርቻለሁ በሚል ከመደበኛ ሥራ መቅረት ወይም መዘግየት በጥብቅ የተከለከለ ነው።
• በሥራ ክፍል አልጋ ማስገባትና በስራ ሰዓት ወጥቶ መጥፋት ተጠያቂነት ያስከትላል።
📅 3. የተገቢነት ጊዜ፦
መመሪያው ከሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የፀና ሲሆን፣ በስታንዳርዱ መሰረት የተሰራው የስምሪት አሰራር ደግሞ ከመስከረም 1 ቀን 2019 ዓ.ም ጀምሮ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ይደረጋል።
መመሪያው ከላይ ተያይዟል።
#WasuMohammed
👇እዚህ ድምፅ ይስጡ👇
https://yekinlibochaward.org/nominees/wasu-mohammed
====================
ወቅታዊ እና የታመኑ መረጃዎች እንዲደርሱዎ የቴሌግራም ቻናሉን join በማድረግ በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
87
7
6
4
4
3
2
2
2
1September 3, 2026 22.9K 87




