በጆሯችን በር በኩል አልፈው በልባችን ላይ የታተሙ የተመረጡ ነባር የነሺዳ ግጥሞችን፤ ከአዳዲስ የግጥም ሥራዎች… — Minber TV — TG.ME

በጆሯችን በር በኩል አልፈው በልባችን ላይ የታተሙ የተመረጡ ነባር የነሺዳ ግጥሞችን፤ ከአዳዲስ የግጥም ሥራዎች ጋር አጣምሮ «በሰማያት በሮች» በኩል ብቅ ያለው የገጣሚ መሐመድ ፈረጅ አዲስ መጽሐፍ መስከረም 01/2019 በግራንድ ኤልያና ሆቴል ከቀኑ 10:30 ጀምሮ ይመረቃል።

​እርስዎም ቅድመ ህትመት መጽሐፉን ለማዘዝ አሊያም በምረቃ ምሽቱ ለመታደም የሚያስችልዎን የመግቢያ ኮድ ቁጥር በሚንበር ሱፐር አፕ (Minber Super App) ላይ ክፍያ በመፈፀም ማግኘት ይችላሉ።

ያስታውሱ ​በዚህ ልዩ የጥበብና የእራት ምሽት ላይ ከእኛ ጋር በመገኘት፤ ደስታችንን እንዲጋሩ በክብር ተጋብዘዋል!

#የመጽሐፍ_ምርቃት #የሰማያት_በሮች #የነፍስ_እንጉርጉሮ #መሐመድ_ፈረጅ
❤24👍8
August 28, 2026 3.2K