የኮማንዶ ክፍለ ጦር በማንኛውም ጊዜ የሚሰጠውን ግዳጅ ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን አሥታወቀ፡፡
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 27 ቀን 2018 ዓ.ም
የኮማንዶ ክፍለ ጦር አዛዥ ኮሎኔል ሰለሞን ፀጋዬ ክፍለ ጦሩ በቅርቡ የጥፋት ኃይሎችን በመመንጠር ያስመዘገበው ታላቅ ድል፣ የሀገርን ሰላምና ሉዓላዊነት ለማስከበር ያለውን ፅናት ያሳየበት መሆኑን ገልፀው ይህ ውጤቱ ወታደራዊ ግዳጅን በስኬት መወጣት ብቻ ሳይሆን፣ የአባላቱን የላቀ የውጊያ ጥበብ በሚገባ ያሳዬ ነው ብለዋል።
ክፍለ ጦሩ እጅግ አስቸጋሪ በሆኑ መልክዓ ምድር ውስጥ የጠላትን የጥፋት መረብ በመስበር እና በመበጣጠስ ረገድ የነበረው ሚና የተጣለበትን ሀገራዊ ግዳጅ የመፈፀም አቅሙን ያረጋገጠበት ነው ያሉት አዛዡ ይህ በውጤት የታጀበ ስምሪት፣ የክፍለጦሩ ሠራዊት በአካልና በታክቲክ የደረሰበትን ከፍተኛ የብቃት ደረጃ ያሳየ እንደሆነ ገልፀዋል።
ኮሎኔል ሰለሞን ፀጋዬ የክፍለጦሩ ሠራዊት ወትሮ ዝግጁነት ባረጋገጠበት ወቅት የክፍለ ጦሩ አስደማሚ ድልና ለአፍታም ቢሆን የማይላላው ወታደራዊ ዝግጁነት አስተማማኝ የሀገር ደህንነት ዋስትና መሆኑን በድጋሚ ያረጋገጠበት ደማቅ ገፅታ እንደሆነ አብራርተዋል፡ዘገባዉ የክፍለ ጦር የሠራዊት ስነ ልቦና ግንባታ ነው
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
https://dfmc.mod.gov.et/
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
https://www.facebook.com/fdredefense.official
47
2
2September 2, 2026 3.7K 1