ዩአፋ በጂያኒ ኢንፋንቲኖ የዓለም ዋንጫ የግል ኢንቨስትመንት ዕቅድ ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ አሰማ።
የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር ፣ ፊፋ ውድድሮቹን፣ የዓለም ዋንጫን ጨምሮ፣ ለግል ባለሀብቶች ክፍት ለማድረግ ያቀደውን ዕቅድ አጥብቆ ተቃወመ።
ፊፋ "ፊፋ ፎርዋርድ ኢንተርፕራይዝ የተባለ አዲስ ቅርንጫፍ ኩባንያ በማቋቋም በንግድ እና በውድድር ስራዎቹ ላይ አነስተኛ እና ውሳኔ ሰጪ ያልሆኑ የሶስተኛ ወገን ኢንቨስትመንቶችን ለመጋበዝ አቅዷል።
የአሜሪካ የቬንቸር ካፒታል ድርጅት የሆነው ትራይቭ ኤተርናል የታቀደውን የባለሀብቶች ቡድን ይመራል ተብሎ ይጠበቃል።
ዩኤፋ በሰጠው ጥብቅ መግለጫ የእግር ኳስ ነፍስ እና አስተዳደር ሊነግዱባቸው የሚገቡ ንብረቶች አይደሉም ብሏል። ይህ ዕቅድ "መቼም ቢሆን መታለፍ የሌለበትን መስመር የተሻገረ ነው" በማለት ፊፋ ውድድሮችን በማስፋፋት እና ድግግሞሻቸውን በመጨመር የራሱን ውድድሮች ሊያስተጓጉል እንደሚችል ስጋቱን ገልጿል።
ጉዳዩ በሚቀጥለው መኸር በሚደረገው የፊፋ ካውንስል ስብሰባ እና በታህሳስ ወር በሚካሄደው የፊፋ አህጉር አቀፍ ዋንጫ ላይ የሚነሳ ሲሆን፣ በመጋቢት ወር በሞሮኮ በሚካሄደው የፊፋ ኮንግረስ ላይ በ211ቱ አባል ሀገራት ድምጽ ሊሰጥበት ይችላል።


















