ለአንድ ወር ያህል ሲካሄድ የቆየው አገራዊ የምክክር ጉባኤ የመዝጊያ ሥነ-ሥርዓት
++++++++++++++
#ጋዜጣ_ ፕላስ- ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ሲካሄድ የቆየው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የመዝጊያ ሥነ-ሥርዓት በአዲስ አበባ ኮንቬንሽን ማዕከል በይፋ እየተከናወነ ይገኛል።
በኢትዮጵያ ሕዝብ መዝሙርና በሃይማኖት አባቶች ጸሎት በተከፈተው በዚህ የመዝጊያ ሥነ-ሥርዓት ላይ የሃይማኖት አባቶች፣ የቀድሞ እና የአሁኑ የአገሪቱ ፕሬዚዳንቶች፣ እንዲሁም ሌሎች ከፍተኛ የአገር መሪዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
በጉባኤው ላይ ከተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የተወጣጡ 4 ሺህ ተሳታፊዎች በተገኙበት በስምንት አጀንዳዎች ላይ ላለፉት ሳምንታት ሰፊ ውይይት ሲደረግ ቆይቷል።
#ጋዜጣ_ፕላስ #ሀገራዊ_ምክክር #አዲስ_አበባ #NationalDialogue #ኢትዮጵያ_ፕሬስ_ድርጅት #ኢትዮጵያ
5August 22, 2026 1.7K




