ለአዲስ ዓመት በዓል ገበያ በቂ ዝግጅት ተደርጓል አለ የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ
የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ በመጪው አዲስ ዓመት በዓል ገበያ ላይ ከፍተኛ ፍላጎት የሚታይባቸውን መሰረታዊ የምግብ ምርቶች በቂ አቅርቦት ማዘጋጀቱን አስታወቀ።
የቢሮው ኃላፊ ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ ዛሬ በሰጡት መግለጫ፤ ከ3 ነጥብ 7 ሚሊዮን ሊትር በላይ የምግብ ዘይት፣ ከ708 ሺህ ኩንታል በላይ ቀይ ሽንኩርት እና 227 ሺህ ኩንታል በላይ ጤፍ ለበዓሉ ገበያ እንደሚቀርብ ተናግረዋል።
በተጨማሪም ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ዶሮዎች፣ ከ42 ሚሊዮን በላይ እንቁላሎች፣ እንዲሁም 2 ሚሊዮን የሚጠጉ በግና ፍየሎች ለገበያ እንደሚቀርቡ ታውቋል።
ምርቶቹን ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ ለማዳረስም 5 የቀንድ እንስሳት መሸጫ ማዕከላት እና 264 የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች በሳምንቱ ሙሉ ክፍት ሆኖ እንዲሰሩ መወሰኑን የቢሮው ኃላፊ ገልጸዋል።
በተጨማሪም ለህብረተሰቡ በጥራትና በበቂ ሁኔታ ለማዳረስ ሲባል የሰብል፣ የአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም የፋብሪካ ምርቶች መሸጫ ማዕከላት አገልግሎቱ እንዲሰጡ ይደረጋል ተብሏል።
ሊዲያ ደሳለኝ
ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም
September 1, 2026 1.8K 5