update በሳዑዲ አረቢያ አንድን ኢትዮጵያዊ በድብደባና በአሰቃቂ ሁኔታ የገደሉ 5 ኢትዮጵያውያን በቁጥጥር… — ETHIO-MEREJA® — TG.ME

ETHIO-MEREJA®#tiktok በሳዑዲ አረቢያ በቀጥታ የማኅበራዊ ሚዲያ (ቲክቶክ) ስርጭት ላይ የግድያ ወንጀል ፈጽሟል የተባለ ኢትዮጵያዊ ከአምስት ግብረ አበሮቹ ጋር በሳዑዲ የጸጥታ አካላት መያዛቸውን በሪያድ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታወቀ። ኤምባሲው እንዳለው፣ በሳዑዲ ድንበርና በረሃማ አካባቢዎች በአንዳንድ ኢትዮጵያውያን መካከል ግጭትና ግድያ መፈጸሙን ተከትሎ ጉዳዩ በቅርበት ሲከታተል ቆይቷል። በተጨማሪም ጉዳዩን…
#update በሳዑዲ አረቢያ አንድን ኢትዮጵያዊ በድብደባና በአሰቃቂ ሁኔታ የገደሉ 5 ኢትዮጵያውያን በቁጥጥር ሥር ውለዋል።

➠ሳዑዲ አረቢያ ውስጥ ወንጀል ፈጽሞ መገኘት እስከ ስቅላት ሞት የሚያደርስ ቅጣት ሊያስፈርድ ይችላል።

የሳዑዲ አረቢያ፣ መካ ፖሊስ የድንበር ደህንነት ሕግን በመተላለፍ ሌላኛውን የኢትዮጵያ ዜጋ ወገናቸውን በከፍተኛ ድብደባ እና በአሰቃቂ ሁኔታ ህይወቱ እንዲያልፍ ያደረጉ 5 የኢትዮጵያ ዜጎችን በቁጥጥር ሥር ማዋሉን አስታውቋል።

እንደ ፖሊስ መግለጫ ተጠርጣሪዎቹ ግለሰቡን ሲደበድቡ ፣ ሲያሰቃዩ የሚያሳይ ቪዲዮ በመሰራጨቱ ፈጣን ክትትል ተደርጎባቸው በራንያ ግዛት ውስጥ በቁጥጥር ሥር ውለዋል።

" ሟችም ሆነ ተጠርጣሪዎቹ የሀገሪቱን የድንበር ደህንነት ሕግ ጥሰዋል " ሲል ፖሊስ ገልጿል።

ፖሊስ በጉዳዩ ላይ አደረኩት ባለው የማጣራት ስራ በተጠርጣሪዎቹ እና በሟቹ መካከል ከዚህ ቀደም የነበረ አለመግባባት የነበረ ሲሆን፣ ሁኔታው ተባብሶ ወደ አዘግናኝ ጥቃት አምርቷል።

የመካ ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹ ላይ ሕጋዊ እርምጃ ለመውሰድ አስፈላጊው የምርመራ ሥራ ተጠናቆ ጉዳዩ ወደ ሌላኛው የሕግ አካላት መተላለፉን ገልጿል።

ሳዑዲ አረቢያ ውስጥ ወንጀል ፈጽሞ መገኘት እስከ ስቅላት ሞት የሚያደርስ ቅጣት ሊያስፈርድ ይችላል። አይደለም የሰዎችን ህይወት ያጠፉ የአደንዛዥ እጽ ዝውውር ላይ የሚሳተፉ በሞት የሚቀጡበት ሀገር ነው።

ነሐሴ 27 ቀን 2018 ዓ/ም



      -ETHIO-MEREJA-
     T.me/ethio_mereja
❤32🤔3
September 2, 2026 3K