ሰሙነ ሕማማት ❤️ ሰኞ ❖ መርገመ በለስ የተፈጸመበት በዚህ ዕለት ጌታችን ከቢታኒያ ሲወጣ ተራበ ፤ ቅጠል… — አርያም ስቱዲዮ _ Areyam Studio — TG.ME

❤️ ሰሙነ ሕማማት ❤️

            ሰኞ

መርገመ በለስ የተፈጸመበት

በዚህ ዕለት ጌታችን ከቢታኒያ ሲወጣ ተራበ ፤ ቅጠል ያለባትን በለስ ተመልክቶ ወደ በለሲቱ ቢቀርብ ከቅጠል በቀር ምንም ነገር ባለማግኘቱ “ከአሁን ጀምሮ ለዘላለም ምንም ካንቺ ፍሬ አይበላ” ማር ፲፩፥፲፬ በማለት ስለረገማት መርገመ በለስ የተፈጸመበት ሰኞ ይባላል።

አንጽሖተ ቤተ መቅደስ ይባላል

ጌታ ወደ ቤተመቅደስ ሄዶ በቤተመቅደሱ የሚሸጡትን እና የሚለውጡትን “ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች” ማቴ ፳፩፥፲፫ በማለት ከቤተመቅደስ ገርፎ አስወጥቷቸዋልና።
April 14, 2025 508