የኢየሱስ ትንሣኤ* ✍️ “እንግዲህ ልጆቹ በሥጋና በደም ስለሚካፈሉ፥ እርሱ ደግሞ በሞት ላይ ሥልጣን ያለውን… — Sonship in Christ — TG.ME

*የኢየሱስ ትንሣኤ*

✍️ “እንግዲህ ልጆቹ በሥጋና በደም ስለሚካፈሉ፥ እርሱ ደግሞ በሞት ላይ ሥልጣን ያለውን በሞት እንዲሽር፥ ይኸውም ዲያብሎስ ነው፥ በሕይወታቸውም ሁሉ ስለ ሞት ፍርሃት በባርነት ይታሰሩ የነበሩትን ሁሉ ነጻ እንዲያወጣ፥ በሥጋና በደም እንዲሁ ተካፈለ።”ዕብራውያን 2፥14-15
መዳናችን ወይም በሞት ላይ ድል ማድረጋችን የመጣው በኢየሱስ ክርስቶስ ሞት ነው። ኢየሱስ ባይሞት ኖሮ የተዋጀን ወይም ከኃጢአትና ከሞት ነፃ አንወጣም ነበር። መዳናችን ስለተሠቃየ አይደለም፣ ስለተደበደበ ወይም በመስቀል ላይ ስለ ተሰቀለ አይደለም። እኛ ድነናል ምክንያቱም ሞቶ ተነሥቷል። የኢየሱስ ሞት እና ትንሳኤ በእኛ ቤዛነት ሂደት ውስጥ ሁለቱ ጉልህ ነገሮች ነበሩ።

✍️ኢየሱስ እንዲሞት እና እንዲሁም የነቢያት ትንቢት እንዲፈጸም የኢየሱስ መደብደብ እና መከራ ሁሉ አስፈላጊ ነበር። ግን ከእነዚህ መከራዎች ውስጥ አንዳቸውም እኛን ለማዳን በቂ አልነበሩም። ኢየሱስ ለብዙ ሰዓታት ደምን ቢፈስስ፣ ሳይሞት በመስቀል ላይ ቢሰቀል መዳን አይኖርም ነበር። መዳናችን በሞቱ፣ በመቃብሩና በትንሣኤው ነው። ይህ የድኅነት ወንጌል ነው። የመዋጀት ሂደታችን ቁንጮ እርሱ መነሳቱ ነው።

✍️ ኢየሱስ ስለ እኛ እንዲሞት እና እንዲነሳ ተፈልጎ ነበር። በእውነት ኢየሱስ በመንፈስና በሥጋ ሞተ። የሞቱና የትንሣኤው ምስክሮች ነበሩ። የኢየሱስ ሞት ግድያ ወይም የአጋጣሚ ሞት አይደለም፣ ሞቱ መስዋዕት ነው። ለመዳን ራሱን ሊገድል አቀረበ። እርሱ ስለ ኃጢአታችን የታረደው የእግዚአብሔር በግ ነው።

*ኢየሱስ ለኃጢአቴ እንደሞተ አምናለሁ። ስለዚህ ከኃጢአት ኃይል ነፃ ነኝ። በዲያብሎስ ላይ ድል አለኝ።
ሉቃስ 23፡44-49
ዮሐንስ 10፡17-18
1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 15፡1-4

ይቀላቀላሉንhttps://t.me/TheimageofChrist1
ለሌሎች 👉👉shareማድረግን እና #Add👈👈 ማድረግን አትርሱ
👍3❤2🥰1
August 16, 2025 520