👉መኖሪያ ቤት ግዥ ሲፈፀም ትኩረት መደረግ ያለባቸው ጉዳዮች
🏛ማንኛውም መኖሪያ ቤት ግዥ ሲፈፅሙ ትኩረት ማድረግ ያለባችሁ ጉዳዮች የሚከተሉት ናቸው፡፡
➜ በመጀመሪያ ይዞታው ህጋዊ ካርታ (የይዞታ ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት)ና ህጋዊ ፕላን ያለው መሆን አለበት፡፡
➜ በሻጭ እጅ ያሉ ሰነዶችና በክ/ከተማው በመዝገብ ቤት በሻጭ ስም ያለ የይዞታ ማህደር ጋር ሰነዶች በትዩዩ አንድ አይነት መሆናቸውን ማረጋገጥ፡፡ በተለይም በካርታው ላይ ያለው የካርታ ቁጥርና በክ/ከተማ መዝገብ ቤት ያለው ቀሪ ካርታ ቁጥር ተመሳሳይ መሆን አለበት፡፡
➜ የይዞታ ማህደሩ ከእዳ፣እገዳና ሌሎች ክልከላዎች ነፃ መሆኑን ማረጋገጥ ይገባል፡፡ የሊዝ እዳ ገዥው እስከ እዳው መግዛት የሚፈልግ ከሆነ እዳውን ማስተላለፍ ይቻላል፡፡
➜ ትዳር ያለው ከሆነ ከወሳኝ ኩነት የትዳር ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት፡፡ ትዳር የሌለው ከሆነ ይህንን የሚያረጋግጥ መረጃ ያስፈልጋል፡፡
➜ ህጋዊ የሽያጭ ውል ከፍትህ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
➜ በውክልና የሚሻሻጡ ከሆነ ውክልናው ህጋዊ መሆኑን ውክልና ከሰጠው የፍትህ ተቋም ማረጋገጥ ይቻላል፡፡
➜ በተጨማሪም በአካል ወደ ሚሸጠው ቤት ሂዶ ቤቱን በአካል ማየትና ማረጋገጥ ተገቢ ነው፡፡
➜ ከመሬት አጠቃቀም ጋር በተያያዘ ማለትም ይዞታው ወደ ፊት ለመኖሪያ ወይስ ወደ ንግድ መቀየር ይቻላል የሚለውን ሀሳብና ከግንባታ ከፍታ ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን በዘርፉ ያሉ ባለሙያዎችን ማማከርና ማረጋገጥ ይቻላል፡፡
@etcon0

6
3September 6, 2026 2K 18