በአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ፍራንክ ጋርሺያ ወደ ኢትዮጵያ ሊያቀኑ ነው።
ጋርሺያ ባለፈው ግንቦት ወር ከተሾሙ ወዲህ ኢትዮጵን ሲጎበኙ የአሁኑ የመጀመሪያቸው ይሆናል።ፍራንክ ጋርሺያ ወደ አዲስ አበባ የሚያቀኑት አገራቸው አሜሪካ የኢትዮጵያ ፌድራል መንግሥትና የትግራይ ክልል ውጥረት እንዲረግብ ከፍተኛ ጥረት እያደረገች በምትገኝበት ወቅት ነው።
ረዳት ሚኒስትሩ በጉዟቸው ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ዛምቢያና ኬንያን እንደሚጎበኙ በአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የአፍሪካ ጉዳዮች ቢሮ ዛሬ ቅዳሜ ነሐሴ 23 ቀን 2018 በኤክስ በኩል አስታውቋል።በቢሮው መረጃ መሠረት የጋርሺያ ጉብኝት “ቁልፍ የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን ለማጠናከር፣ የጋራ ኢኮኖሚያዊና የደሕንነት አጋርነቶችን ለማሳደግ” ያለመ ነው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter

5
5August 29, 2026 3.5K