ነገራችን ወሬ ብቻ እንዳይሆን!
“ስለ አንድ ነገር የምታወሩ ከሆነ ነገሩ ህልም ይባላል፣ ስለነገሩ በሚገባ ማሰብ ስትጀምሩ ነገሩ ወደመቻል ይሸጋገራል ማለት ነው፣ ለነገሩ የጊዜ ሰሌዳ ካዘጋጃችሁለት ግን ነገሩ እውን ወደመሆን ይመጣል” - ANTHONY ROBBINS
• ቁጭ ብላችሁ ወደማሰብና ስለነገሩ ወደማሰላሰል ያልደረሰ እስካሁን በወሬ ብቻ የቀረውን ነገር እስቲ ለማስታወስ ሞክሩ!
• ካሰባችሁና ካሰላሰላችሁት በኋላ ወደ እርምጃ እና ወደ እንቅስቃሴ ለመግባት የጊዜ ገደብና ሰሌዳ ያላስቀመጣችሁለትንም ነገር እስቲ አስቡት!
ነገሮቻችሁ ከወሬ አልፈው ሃሳባችሁን እንዲገዙት፣ ከሃሳብ አልፈው ደግሞ ወደ እውነታ እንዲመጡ ከፈለጋችሁ ይህንን መርህ መገንዘብ አስፈላጊ ነው፡፡
ንግግራችን ረገብ፣ ሃሳባችሁን ሰፋ፣ እቅዳችሁ ደግሞ ተግባራዊ በማድረግ ልቃችሁ ተገኙ!
መልካም ምሽት
2
2
1August 20, 2026 218 1