ᴅᴀɪʟʏ ʜᴀᴅɪᴛʜ✨ ❴Part 281❵ #hadith281 "የአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) የኸይበር ዕለት… — 𝐇𝐚𝐟𝐮 𝐢𝐬𝐥𝐚𝐦𝐢𝐜 𝐩𝐨𝐬𝐭™🕋 — TG.ME

𝐇𝐚𝐟𝐮 𝐢𝐬𝐥𝐚𝐦𝐢𝐜 𝐩𝐨𝐬𝐭™🕋✨ᴅᴀɪʟʏ ʜᴀᴅɪᴛʜ✨ ❴Part 280❵ #hadith280 "አቡ ሁረይራ(ረ ዐ)እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ (ሰ ዐ ወ)እንዲህ ብለዋል።ሰባት (ፈታኝሁኔታዎችሳይገጥማችሁበፊት)ለመልካም ተግባራትተሽቀዳደሙ።ወደ ፊት የሚጠብቃችሁ አዘናጊ የሆነድህነት ወይም ለአመጽና ወንጀለኝነት የሚዳርግ ሀብት ፣በካይ የሆነ በሽታ፣ወይም የሚያጃጃ እርጅና፣አጣዳፊ ሞት ፣ክፉው ይመጣል ተብሎ የሚጠበቀው ደጃል ፣ወይም ወሰን…
ᴅᴀɪʟʏ ʜᴀᴅɪᴛʜ

❴Part 281❵ #hadith281


"የአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) የኸይበር ዕለት "ይህንን ሰንደቅ አላህንና መልዕክተኛውን በእጀጉ ለሚያፈቅር ሰው እሰጣለሁ፡፡ አላህ በዚህ ሰው እጅ ለድል ያበቃናል" አሉ። ዑመር (ረ.ዐ)፡- "ከዚያን ቀን ውጪ ሹመትን ተመኝቼ አላውቅም፡፡ (የዚህ ታላቅ እድል ባለቤት በመሆን) እጠራ ይሆናል በሚል ተስፋ እንንጠራራ ነበር -(ለመታየት)፡፡ የአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) ዐሊይን(ረ.ዐ) ጠሩ፡፡ ሰንደቅ አላማውንም አስረከቡት፡፡ "አላህ ለድል እስኪያበቃን ድረስ ወደፊት ቀጥል፡ ወደሗላ አትዙር" አሉትም፡፡" ብለዋል ዐሊይ (ረ.ዐ) ጥቂት ተጓዘናቆመ፡ ወደሗላ አልዞረም፡፡ " የአላህ መልዕክተኛ ሆይ!ሰዎችን የምዋጋቸው ለምን ዓላማ ነው?" ሲል ጠየቀ፡፡ ከአላህ ውጪ ሌላ አምላክ አለመኖሩንና ሙሐመድም የአላህ መልዕክተኛ መሆናቸውን አስኪመሰክሩ ድረስ ተፋለማቸው። ይህንን ካደረጉ ደማቸው፥ ገንዘባቸውም፥ ህጋዊ በሆነ መልኩ ካልሆነ በቀር፥ ካንተ የተጠበቀ ነውሌሎች ተግባሮቻቸውን መተሳሰብ ከአላህ ነው" አሉት፡፡

(ሙስሊም ዘግበውታል)



📋ያለፈው ክፍል👇📋
https://t.me/Hafu_posts/17866

🚫ለወዳጆቻችሁ በመላክ ከአጅሩ ተካፈሉ🚫
❤13
August 23, 2026 2.7K 1