Yeka Education: post #5935 — TG.ME

🟣በዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና 563 ሺ 960 ተማሪዎች ተመዝግበው 550 ሺ 210 ተማሪዎች ፈተናውን ወስደዋል። 🟢ፈተናውን ከወሰዱት ውስጥ 12.8 በመቶ የሚሆኑት ተማሪዎች 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ ማምጣት ችለዋል። 🔵ዘንድሮ በአጠቃላይ ፈተናውን ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል ማለፍ የቻሉት 70 ሺ 544 ናቸው። 🟠ካለፉት መካከል በተፈጥሮ ሳይንስ 16.5 በመቶ ሲሆኑ በማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ 8.33 በመቶ ናቸው 🟪ከፍተኛ ውጤት ! በተፈጥሮ ሳይንስ ወንድ 591.6 ከ600 ተመዝግቧል። ተማሪው የኦዳ ስፔሻል ቦርዲንግ - አዳማ ተማሪ ነው። ከሴት ደግሞ 583 ከ600 ሲሆን ከእንጅባራ አገው ምድር ትምህርት ቤት ነው። • 576.25/600 — ማህበራዊ ሳይንስ፣ ወንድ — ዶዶላ ኢፋ ቦሩ ትምህርት ቤት • 569/600 — ማህበራዊ ሳይንስ፣ ሴት ዋና ዋና መረጃዎች 🌔565 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ ማሳለፍ አልቻሉም። 🌔 100% ያሳለፉ ትምህርት ቤቶች • አምና — 62 • ዘንድሮ — 88 🌍 በፈተና አሰጣጥ ዘዴ • በኦንላይን የተፈተኑ — 18.37% አልፈዋል። • በወረቀት የተፈተኑ — 4.2% አልፈዋል። 🌒 በአጠቃላይ፦ የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የማለፊያ ምጣኔ 12.8% ሲሆን፣ አዲስ አበባ 32.4% በማስመዝገብ ከፍተኛውን የክልል ደረጃ ይዟል። በተጨማሪም 100% ያሳለፉ ትምህርት ቤቶች ከ62 ወደ 88 ከፍ ብለዋል።

❤98🔥13🙏12👏9🏆6👍1👌1
August 22, 2026 29.8K 217