ይህን ድንቅ ታሪክ በፍፁም ሳያነቡ እንዳያልፉ
አላህ (ሱ.ወ) ባደረከው ነገር ይደነቃል
አቡ ሁረይራህ (ረ.ዐ) እንዲህ ብለዋል፡- ከእለታት “አንድ ቀን አንድ ሰው ወደ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ዘንድ መጣና “ችግር ውስጥ ነኝ ርቦኛል፣ ገንዘብም ሆነ የምበላው ነገር የለኝም )” አላቸው።
ከዚያም ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ሰውየውን ወደ እያንዳንዱ ሚስቶቻቸው ቤት አመጡትና፣ ምግብ አለን ወይ ብለው ጠየቁ።
ሁሉም ሚስቶቻቸው "በእውነተ በላከህ አላህ እምላለሁ ከውሃ ውጪ ምንም የምንበላው ነገር የለንም" እያሉ ሀሉም ይህን መልስ ሰጡ ።
ከዚያም ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ለባልደረቦቻቸው እንዲህ አሉ፡- “ይህን ሰው በቤቱ በእንግድነት ሊጋብዘው የሚችል ሰው አለ ይህን የሚያረግ ሰው ካለ እርሱ በእርግጥ አላህ ዘንድ ይባርካል አሉ ።
ከዚያም ከባልደረቦቻቸው መካከ አንድ ሰው ቆሞ
አንቱ የአላህ መልእክተኛ ሆይ ይህን ሰው እኔ ቤት ወስጄ በእንግድነት እጋብዘዋለው አለ።
ከዚያም ሰውየውን ወደ ቤቱ አመጣውና ሚስቱን የሚበላ ነገር አለ ወይ ብሎ ጠየቀ
? እሷም “ከልጆቻችን ምግብ በስተቀር ምንም የለም” ብላ መለሰች።
እርሱም፡ “ ልጆቻችንን በሥራ አስጠምጂያቸውና (ምግቡን እንዲረሱ አድርጊ)። እንግዳችን ወደ ቤታችን ሲገባ ከእርሱ ጋር እንደምንበላ እናስመስል። ከዚያም ምግቡን ልንበላ ስንል ተነስተሽ ኩራዙን። አጥፊው አለ
ለሁላችንም የሚበቃ ምግብ ስለሌለ ከእርሱ ጋር እንደማንበላ አያውቅም)። እንግዳው ወደ ቤት ሲገባ፣ ሚስት ባሏ እንድታደርግ የነገራትን በትክክል አደረገች።
ከሰሀባዎች እንዱ በጠዋት ወደ እነርሱ ዘንድ መጣና ፈገግ ብሎ “ትላንትና ማታ እንግዳህን የተቀበልክበትን መንገድ አላህ ተደንቋል አለው ።
የታሪኩ መልእክት የእራሱን ሃብት መስዋእት ማድረግ ቢሆንም ለተቸገሩት እንግዳ ተቀባይ እና ለጋስ መሆን ነው።
ሰውየው እና ሚስቱ ውስን ምግብ ቢኖራቸውም እንግዶቻቸውን ሳይሳቀቁ ምቾት የሚያገኙበት መንገድ ስላገኙ ሌሎችን በማገልገል ላይ የፈጠራ እና የጥበብን አስፈላጊነት አጉልቶ ያሳያል ።
ታሪኩ ሩህሩህ እና እንግዳ ተቀባይ እንድንሆን ያበረታታናል፣
https://t.me/bedru511111
March 20, 2025 3.5K 16