➽አንበሳ ባስ ውስጥ ዋሌቱን ከ( 300 )ብር ጋር በቅፅበት የተሰረቀው ግለሰብ ድምፁን ከፍ አድርጎ እንዲህ እያለ ሲጮህ ተደመጠ ➽ኢኸው ተናግሪያለሁ ! ዋሌቴን አሁን እዚሁ ነው የተሰረቅኩት ብትመልሱልኝ ይሻላችኋል አለ ። በባስ ውስጥ የተሳፈሩት ሀሉ በአንድ ጊዜ ወደ ሰውየው ዘወር ብለው ተመለከቱ ➽ሰውየው ቀጠለና አሁኑኑ ካልመለሳችሁልኝ ህዳር 14 /1993 / ዓ.ም አባቴ የሠራውን ታሪክ እደግመዋለሁ" በማለት በቁጣ ተናገረ ➽ተሳፋሪዎቹ በሙሉ በሰውየው ሁኔታ ተደናገጡ !! ሰውየው ቀጠለና አባቴ ይሙት ባሱ ሳይንቀሳቀስ ህዳር 14/1993/ የሞተውን የአባቴን ታሪክ እንዳልደግመው ለመጨረሻ ጊዜ ተናግሪያለሁ እያለ ሲዝት 5 ደቂቃ ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ዋሌቱን ገልጦ ለማየት እንኳን ፋታ ያላገኘው ፍሬሽ ሌባ መሬት ላይ ይጥለውና እራሱ አንስቶ "ይሄው ዋሌትህ" በማለት ይመልስለታል። ➽ባሱ ውስጥ የነበሩ በእድሜ ገፋ ያሉ ተሳፋሪዎችም እሰይ ፣እሰይ ተመስገን ሊጨርሰን ነበር" እኮ እየተባበሉ አውቶብሱ ጉዞውን ቀጠለ። ➽የባሱ ተሳፋሪዎች ሰውየው መረጋጋቱን ካስተዋሉ በኋላ የ 14/1993/ ቱን ታሪክ ለመስማት ቋምጠው ነበርና ከተሳፋሪዎቹ የተወሰኑት በ 1993 ህዳር 14 አባትህ ምን ነበር ያደረጉት እባክህ በማለት ፈራ ተባ እያሉ ጠየቁት ? ➽ነፍሱን ይማረውና አባቴ ዛሬ በህይወት የለም። ነገር ግን ህዳር 14/1993/ ላይ እንዲህ እንደኔ አንበሳ ባስ ወስጥ ለመሳፈሪያ እንኳን ሳያስቀሩለት ሌቦች ገንዘቡን ሰርቁት እና ተሰወሩ ➽አባቴም ጃኬቱን እንደ እብድ እያውለበለበ ከሳር ቤት ፈረንሳይ ድረስ በእግሩ ነበር የሄደው። ➽እኔም ዛሬ ብሬን ባትመልሱልኝ ኖሮ ያው የታክሲም ስለሌለኝ በእግሬ ወደ ቤቴ በመሄድ የአባቴን ታሪክ እደግመው ነበር" ብሏቸው እርፍ፡፡
አንበሳ ባስ ውስጥ ዋሌቱን ከ( 300 )ብር ጋር በቅፅበት የተሰረቀው ግለሰብ ድምፁን ከፍ አድርጎ እንዲህ… — ALAJE TIMES — TG.ME
May 6, 2024 1.7K 2