ቴንሃግ እና ሰራዊታቸው አሳዛኝ ታሪክ መጻፋቸውን ቀጥለዋል😞😔 ❌ ማንቸስተር ዩናይትድ በኤፍ.ኤ ውድድር… — Sport News/ስፖርት ዜና — TG.ME

ቴንሃግ እና ሰራዊታቸው አሳዛኝ ታሪክ መጻፋቸውን ቀጥለዋል😞😔

ማንቸስተር ዩናይትድ በኤፍ.ኤ ውድድር ከታችኛው እርከን በመጡ ክለቦች 2 እና ከ2 በላይ ግብ ሲቆጠርበት ከየካቲት 1996 በኋላ ለመጀመርያ ጊዜ ነው። በ1996 ዩናይትድ ከሰንደርላንድ ጋር ካደረገው ግጥሚያ በኋላ እንደዚህ አይነት ውጤት አስመዝግቦ የማያውቅ ሲሆን፡ በትላንትናው የኒውፖርት ጨዋታ ይህን ታሪክ ማጻፍ ችሏል።

በተጨማሪም ለመጀመርያ ጊዜ ከ4ኛ ዲቪዚዮን ቡድን ጋር ተጫውቶ 2 እና ከዝያ በላይ ግብ ሲያስተናግድ ከየካቲት 1970 ከኖርዝሃምፕተን ጋር ካደረገው ጨዋታ በኋላ ለመጀመርያ ጊዜ ነው።

በእንግሊዝ የእግር ኳስ እርከን፡ ፕሪሚዬርሊግ፣ ቻምፒዮንሺፕ፣ ሊግ 1 እና ሊግ 2 ተብለው የሚከፋፈሉ ሲሆን፡ በትላንትናው ግጥሚያ ዩናይትድን ያስተናገደው ኒውፖርት ካውንቲ የ4ኛው እርከን (ሊግ2) ተሳታፊ ቡድን መሆኑ ይታወሳል።
❤7👍3🥰1👏1
January 29, 2024 4.1K 1