R e a l N o r t h™ 🧭: post #916 — TG.ME

ከላይ የተዘረዘሩትን የወንጌላዊያን አብያተክርስቲያናትን በመሠረታዊ አስተምህሮ አንድ የሚያደርጋቸው ዋን ዋና ነጥቦች

መጽሐፍ ቅዱስ :- የእግዚአብሔር ቃል፣ ከሁሉ በላይ የሆነ የሕይወትና የእመነት መመሪያ ነው።      

ፀጋ :- መዳን በሰው መልካም ስራ ሳይሆን፣ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን ብቻ የሚገኝ የእግዚአብሑእር ስጦታ ነው።

ኢየሱስ ክርስቶስ:- ብቸኛ አዳኝ፣ የሰው ልጆች ሁሉ አማላጅ እና የቤተክርስቲያን ራስ ነው።

ሥላሴ :- እግዚአብሔር  በአብ፣ በወልድ፣ እና በመንፈስ ቅዱስ ሦስት አካልና አንድ አምላክ ነው።

ወንጌል :- ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሞቶ  እንደተነሳ የሚናገረው የምስራች ለዓለም ሁሉ መሰበክ አለበት ።

የኢትዮጵያ ገነት ቤተ ክርስቲያን :- በፊንላንድ ሚስዮን አማካኝነት የተመሰረተች  የጴንጤቆስጤ Pentecostal አስተምህሮን የምትከተል ናት።

ጥምቀት:- የአዋቂ የአማኝ ጥምቀት ብቻ በውኃ ውስጥ በመጥለቅ።

የጌታ እራት:- የጌታ ሞትና ትንሳኤ መታሰቢያ ነው።

ልዩ አስተምህሮ :- በመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች ልሳን፣ ትንቢት ታምናለች።

   ከሌሎቹ ለየት የሚያደርጋት በአስተዳደር ረገድ "ኤጲስ ቆጶሳዊ" Episcopal መዋቅርን ትከተላለች፤ ማለትም የቤተክርስቲያኗ መሪዎች ኤጲስ ቆጶስ" ተበለው ይጠራሉ።

@Real_North
❤3
July 20, 2026 325 1