መረጃ ዘመደመር: post #70409 — TG.ME

#ሁለት_አይነት_አቀራረቦች!

የየእለት ሕይወታችንን በሁለት መልኩ የመቅረብ ምርጫ አለን፡-

1.   “የምላሽ ሰጪነት አቀራረብ” (reactive approach)
ይህ አቀራረብ በአካባቢያችን ለሚከናወኑ ሁታዎች፣ ለስሜታችንና ለሰዎች ሁኔታ ምላሽ እየሰጡ መኖርን ያመለክታል፡፡ ይህንን አቀራረብ የሚለማመዱ ሰዎች ለሕወታቸው ቅድመ-እቅድ ሳይኖራቸው ለመጣው ነገር ምላሽ እየሰጡ የሚኖረ ሰዎች ናቸው፡፡ በውጤቱም፣ ራሳቸውን አይመሩም፣ በሰዎች ላይ ተጽእኖ አያመጡም እንዲሁም ምንም አይነት ስራን አቅደው ሰርተው አያሳድጉም፡፡

2.  “የንቁ አቀራረብ” (proactive approach)
ይህ አቀራረብ በሕይወታችን መሆን እና ማከናወን በምንፈልገው ነገር ዙሪያ ሆን ብሎ አቅዶ መንቀሳቀስን ያመለክታል፡፡ ይህንን አቀራረብ የሚለማመዱ ሰዎች ለሕይወታቸው ግልጽ የሆነ ዓላማ ስላላቸው በዚያ ዙሪያ ግብን በማውጣት፣ በመንቀሳቀስና አልፎ አልፎም ግምገማ በማድረግ ይራመዳሉ፡፡ በውጤቱም፣ ራሳቸውን ይመራሉ፣ በሰዎች ላይ መልካም ተጽእኖ ያመጣሉ፣ ስራቸውንም ያሳካሉ፡፡
August 20, 2026 77