ማንም ያልጠበቀው አስደናቂ ተግባር! በኢራን እና በኒውዚላንድ መካከል ከተደረገው የአቻ ውጤት በኋላ፣ የፊፋው… — Major Crypto Airdrops — TG.ME

ማንም ያልጠበቀው አስደናቂ ተግባር!
በኢራን እና በኒውዚላንድ መካከል ከተደረገው የአቻ ውጤት በኋላ፣ የፊፋው ፕሬዝዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ በድንገት የኢራንን መልበሻ ክፍል በመጎብኘት ለተጫዋቾቹ የድጋፍ መልዕክት አስተላልፏል። ሀገሪቱ በአሁኑ ወቅት እያለፈችበት ባለው አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ለነበሩት ተጫዋቾች ይህ ትልቅ መነቃቃትን ፈጥሯል።

🗣️ “ለቤተሰቦቻችሁ፣ ለጓደኞቻችሁ እና ለመላው ዓለም የዓለም ዋንጫ ተካፋይ መሆን እንደሚገባችሁ በተግባር አሳይታችኋል። እያለፋችሁበት ያለውን አስቸጋሪ ሁኔታ እረዳለሁ፣ ነገር ግን እናንተ ከማንኛውም ፈተና በላይ ጠንካሮች ናችሁ።”

ፕሬዝዳንቱ የቡድኑን አይበገሬነት፣ ጠንካራ ማንነት እና ቁርጠኝነት ያደነቁ ሲሆን፣ በዓለም ዋንጫው ላይ እያሳዩት ያለው ብቃት ከእግር ኳስ ጨዋታም ባለፈ ትልቅ ሰብአዊ መልዕክት እያስተላለፈ መሆኑን ገልጸዋል።

በእግር ኳስ ዓለም ብዙም ያልተለመደ እና የብዙዎችን ቀልብ የሳበ ግሩም ተግባር!
Ebrahim Yezid
👏1
June 17, 2026 27