Falcon Grade 12Social 2017 E.C: post #550 — TG.ME

ማስታወቂያ
የRemedial ፕሮግራም ምደባ እየተጠባበቃችሁ ላላችሁ ተማሪዎች በሙሉ፤
በ2017 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች የተቋም ምደባ ከአሁን ሰዓት ጀምሮ ከታች በተዘረዘሩት አማራጮች ማየት የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን ተቋማት በሚያስተላልፉት ጥሪ መሰረት የ Remedial ፕሮግራሙን እንድትከታተሉ እናሳውቃለን።

የተመደባችሁበትን ተቋም ለማየት የቀረቡ አማራጮች
1. Website: https://student.ethernet.edu.et
2. Telegram bot: @moestudentbot

ትምህርት ሚኒስቴር
October 29, 2025 795 12