በሕይወታችሁ ውስጥ ከባድ ድካም፣ ግራ መጋባት ወይም የመቁረጥ ስሜት ተሰምቷችሁ ያውቃል?
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የነበሩ ታላላቅ የእግዚአብሔር ሰዎችም እንኳን እንዲህ ያለ ጥልቅ ፈተናና ድካም ውስጥ አልፈው ነበር፦
• ኤልያስ በፍርሃት ተሸንፎ፦ "ጌታዬ ሆይ በቃኝ ሕይወቴን ውሰዳት" አለ። (1ኛ ነገሥት 19:4)
• ኤርምያስ በጥልቅ ስሜታዊ ድካም ውስጥ ሆኖ፦ "የተወለድኩባት ዕለት የተረገመች ትሁን" አለ። (ኤርምያስ 20:14)
• ሙሴ በድካም ውስጥ ሳለ፦ "እንዲህስ ከምታደርግብኝ ፈጽሞ ግደለኝ" አለ። (ዘኍልቁ 11:15)
• ኢዮብ ሊቋቋመው በማይችል ሕመም ውስጥ ሆኖ፦ "ስወለድ ለምን አልሞትኩም?" ሲል ተናገረ። (ኢዮብ 3:11)
ነገር ግን አስታውሱ፤ እግዚአብሔር ፈጽሞ የማይተው፣ የተሰበሩ ሰዎችንም እንደገና የሚያስታውስና የሚያነሳ አምላክ ነው!
ዛሬ ድካም፣ ግራ መጋባት ወይም ጥንካሬ ማጣት ከተሰማህ፡ እነሱም እንደዚያ እንደተሰማቸው አስታውስ፤ ነገር ግን እግዚአብሔር አላጣቸውም፣ አልተዋቸውምም።
እግዚአብሔር አሁንም ፈጽሞ ያላበቃውን የታሪክህን ምዕራፍ ሊጽፍ ይችላል! 🙏🤍
✍️ / ዑራኤል
ማንኛውም ሀሳብ
👇👇👇
@Mogesinewokibrene


