ማሳሰቢያ -- የሥራና ክህሎት ሚኒስቴርዜጎች በሃገር ውስጥ እና በውጭ በሚፈጠር የሥራ ዕድል በህጋዊ መንገድ… — Ministry of labor and skills — TG.ME

Forwarded fromZO|| ZOLLA TUBE ||
-- ማሳሰቢያ --

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴርዜጎች በሃገር ውስጥ እና በውጭ በሚፈጠር የሥራ ዕድል በህጋዊ መንገድ መብታቸው ደህንነታቸው እና ጥቅማቸው ተጠብቆ መስራት እንዲችሉ የሰለጠነ እና በከፊል የሰለጠነ የሰው ሃይል ስምሪት ስምምነት በመፈፀም ለፓስፖርት እና ለጤና ምርመራ ከሚከፈል ክፍያ ውጪ በነፃ አገልግሎት እንዲያገኙ እያደረገ ይገኛል፡፡

በዚህ አገልግሎት በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት የባዮሜትሪክስ መረጃዎቻቸውን የሰጡ፣ ማንነታቸው የተረጋገጠ፣ ስልጠና የወሰዱ ከ189,430 በላይ ዜጎች ባለፉት 6 ወራት ወደ ተለያየ ሃገር ተሰማርተዋል፡፡ በስምሪቱ ከፍተኛ ስኬት ያስመዘገቡ ክልሎች እንደሚከተለው ይቀርባሉ፡፡

 ኦሮሚያ ክልል = 94,106
 አማራ ክልል = 39,205
 ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል = 27,500
 ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል = 14,947
 አዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር = 6,331
 ደቡብ ምዕራብ ክልል = 3,613
 ሲዳማ ክልል = 1,430
 ትግራይክልል = 822
 ሐረር ክልል = 286
 አፋር ክልል = 205
 ድሬዳዋ ከተማ መስተዳደር = 193
 ሱማሊ ክልል = 193
 ቤንሻንጉል ክልል = 181
 ጋምቤላ ክልል = 83

በዚህ በውጭ ሃገር የሥራ ስምሪት በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ ዜጎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ አስፈላጊውን ግብዓት በማሟላት ከዚህ በፊት ወደ ውጪ ሃገር ሰራተኛ አሰማርተው የማያውቁ ክልሎች ጭምር የዕድሉ ተጠቃሚ የሚሆኑበትን ምቹ ሁኔታ የፈጠረ በመሆኑ የስምሪቱ ተጠቃሚ መሆን የምትፈልጉ ዜጎች በአቅራቢያቹ በቀበሌ ደረጃ በሚገኙ አንድ ማዕከላት በመሄድ እንድትመዘገቡ ጥሪ እናቀርባለን::

ከዚህ ውጪ የሚደረግ ወደ የትም ሃገር "ለስራ እናሰማራቸዋለን" እና "በቀላሉ ስራ እንድታገኙ እናማክራቸዋለን” የሚል ቅስቀሳ ዜጎችን ለከፋ አደጋ የሚጥል እንዲሁም ከፍተኛ የገንዘብ ማጭበርበር በመሆኑ ራሳቸውን እንድትጠብቁ እናሳስባለን፡፡

የባዮሜትሪክስ ምዝገባ የሚያከናውኑ አንድ ማዕከላትን ዝርዝር (https://lmis.gov.et/ossc-lists ) ከዚህ ላይ ማግኘት ይቻላል፡፡

የሥራ ባለቤት እርስዎ ነዎት!!
👍15👎1
March 6, 2024 2.5K 2 6