የብሬክስሩ አሻሚው የንግድ ሞዴል፤ ሌላው የፒራሚድ ስኪም? "ብሬክስሩ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር (Breakthrough Trading S.C.)" በተመለከተ የ "ሪፖርተር" ጋዜጣ እንግሊዝኛ ዕትም ሰፊ የምርመራ ዘገባ ይዞ ወጥቷል። በዚህ ዘገባ ኩባንያው ባለፉት 6 ዓመታት ከ100,000 በላይ ሰዎችን ማሰልጠኑን ቢገልጽም፣ የኢትዮጵያ ትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን (ETA) ግን ለፕሮግራሞቹ ምንም ዓይነት እውቅና ወይም ፈቃድ እንዳልሰጠ ይገልጻል። ዋና ሥራ አስፈጻሚው ዶክተር ሚልኪያስ አየለ ድርጅቱ የንግድ ፈቃድ ያለውና ግብር የሚከፍል በመሆኑ የሰውነት ማበልጸግ ስልጠና መስጠት ይችላል ቢሉም፣ ፕሮግራሞቹን በባለሥልጣኑ ዘንድ ያላስመዘገቡ መሆኑን አምነዋል። በተጨማሪም በኩባንያው ሰነዶች ላይ NLP እና ሃይፕኖቴራፒ ስልጠና እንደሚሰጥ ቢጠቀስም፣ ዋና ሥራ አስፈጻሚው ግን በነዚህ ዘርፎች ላይ አሰልጣኝ እንደሌላቸውና ስልጠና እንደማይሰጡ ተናግረዋል። ዘገባው ኩባንያው ከ100,000 ሰልጣኞች መካከል ስንቶቹ ዘላቂ ስኬት ላይ እንደደረሱ የሚያሳይ የተረጋገጠ መረጃ ማቅረብ አለመቻሉንም ያመላክታል። ስለ ኩባንያው የቢዝነስ ሞዴል በሚያሳየው ክፍል፣ ሰልጣኞች ከ3,800 እስከ 52,000 ብር የሚያስከፍሉ ከአምስት በላይ የስልጠና ደረጃዎችን እንደሚገዙ ይጠቅሳል። ስልጠናውን ያጠናቀቁ ሰዎች አዳዲስ ገዢዎችን ሲመልመሉ ከ10% እስከ 19% የሰንሰለት ኮሚሽን፣ ከ8% እስከ 15% የቡድን ማሳደጊያ ክፍያ እና በነጥብ የተሰሉ ሽልማቶችን ያገኛሉ። በኩባንያው ሰነዶች ላይም እስከ 500,000 ነጥብ (ከ25,000 እስከ 500,000 ዶላር ግምት ያለው)፣ የመኪና እና የውጪ ጉዞ ማበረታቻዎች ተቀምጠዋል። ይህ አሰራር አዳዲስ ሰዎችን በማስገባት ላይ የተመሰረተ በመሆኑ፣ በንግድ ውድድርና ደንበኞች ጥበቃ አዋጅ ቁጥር 813/2005 አንቀጽ 22(6) ከተከለከለው "የፒራሚድ ስኪም" ጋር እንደሚመሳሰል የሕግ ባለሙያዎች ይሞግታሉ። በተጨማሪም የኩባንያው የውስጥ ደንብ ከደንበኞች ለሚነሱ አቤቱታዎች ተጠያቂነቱን ወደ አባላት/መልማዮች የሚያዞር መሆኑ ተጠቅሷል። በመጨረሻም የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ለስልጠና አገልግሎት የብቃት ማረጋገጫ እንደማይጠይቅ ቢገልጽም፣ የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን (ETA) ክትትል አድርጎ ጥሰት ካገኘ የንግድ ፈቃዱ ሊታገድ እንደሚችል መግለጹ በዘገባው ተካቷል። ©Tikivahmegazine @darashMedia @darashMedia
የብሬክስሩ አሻሚው የንግድ ሞዴል፤ ሌላው የፒራሚድ ስኪም? "ብሬክስሩ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር… — Darash Media — TG.ME
August 26, 2026 11.2K 17