" 2 ቀናት ብቻ ቀሩት!" ውድ የመኖሪያ ቤት አከራዮች እና ተከራዮች፤ ጊዜው እየፈጠነ ነው!! የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ያስቀመጠው የአከራይ ተከራይ የውል እድሳት ጊዜ ሊጠናቀቅ 2 ቀናት ብቻ ቀርተውታል። ለምን ውል ማደስ ያስፈልጋል? ✍ የሁለቱንም ወገን ሕጋዊ መብት ለማስከበር ✍የኪራይ ዋጋ ጭማሪ ደንብን (11.5%) አክብሮ ለመስራት ✍ ከተጨማሪ ቅጣት እና አላስፈላጊ እንግልት ለመዳን አገልግሎቱ የሚሰጥበት ቦታ፦ በየክፍለ ከተማው ቤቶች አስተዳደር ፅ/ቤቶች ፤ በየወረዳው እና በሁሉም የመሶብ አንድ ማእከል አገልግሎት መስጫዎች በሚገኙ የአገልግሎት መስጫ ማዕከላት "አሁኑኑ ውላችሁን በማደስ ሊያጋጥሙ ከሚችሉ አላስፈላጊ ቅጣቶች እና እንግልቶች ራሳችሁን ጠብቁ!”
September 3, 2026 3.3K 4