ለኦርቶዶክሳውያን !
+ አባቶቻችን ነገ ነሐሴ 30 ቀን አስቸኳይ ስብሰባ ያደርጋሉ፡፡
+ ለምን ታዲያ እኛስ እንደ ምእመንነታችን ማድረግ የምንችለውን አናደርግም?
+ ለምን እነርሱ ሲሰበሰቡ እኛም አብረን የዓቅማችንን ያህል በፈቃደኝነት አንጾምም?
+ ለምን የዓቅማችንን ያህል ሌላ ጊዜ ከምንጸልየው በተጨማሪ ጸሎት አናደርስም?
+ አሕዛብ የነበሩ የነነዌ ሰዎች ሊመጣ ከነበረው መዓት በእውነተኛ ንስሐቸው በጾም በጸሎት ከተረፉ፥ ክርስቲያን የኾንን እኛ'ማ እንዲህ እንደ ዓቅማችን ብናደርግ እግዚአብሔር የበለጠ ይሰማናል፡፡
+ ስለዚህ ይህን ጽሑፍ የምታነቡ ወገኖቼ መንግሥት የሚሠራውን በቁዔት የለሽ ድራማ ትተን ይህን ሠናይ ሥራ ብናደርግ መልካም ነው፡፡
@yohansafework
September 4, 2019 7.4K 9