🌅ኦርቶዶክሳዊ_የክርስትና_ሕይወት🌅: post #263 — TG.ME

ለኦርቶዶክሳውያን !

+ አባቶቻችን ነገ ነሐሴ 30 ቀን አስቸኳይ ስብሰባ ያደርጋሉ፡፡

+ ለምን ታዲያ እኛስ እንደ ምእመንነታችን ማድረግ የምንችለውን አናደርግም?

+ ለምን እነርሱ ሲሰበሰቡ እኛም አብረን የዓቅማችንን ያህል በፈቃደኝነት አንጾምም?

+ ለምን የዓቅማችንን ያህል ሌላ ጊዜ ከምንጸልየው በተጨማሪ ጸሎት አናደርስም?

+ አሕዛብ የነበሩ የነነዌ ሰዎች ሊመጣ ከነበረው መዓት በእውነተኛ ንስሐቸው በጾም በጸሎት ከተረፉ፥ ክርስቲያን የኾንን እኛ'ማ እንዲህ እንደ ዓቅማችን ብናደርግ እግዚአብሔር የበለጠ ይሰማናል፡፡

+ ስለዚህ ይህን ጽሑፍ የምታነቡ ወገኖቼ መንግሥት የሚሠራውን በቁዔት የለሽ ድራማ ትተን ይህን ሠናይ ሥራ ብናደርግ መልካም ነው፡፡

@yohansafework
September 4, 2019 7.4K 9