MatricET: post #5068 — TG.ME

ለሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች (ASTU & AASTU) የ2019 ዓ.ም የመግቢያ ፈተና ተፈታኞች በሙሉ!

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በአፕላይድ ሳይንስ እና በኢንጂነሪንግ የትምህርት ዘርፎች በኦንላይን የተመዘገባችሁ አመልካቾች በሙሉ


📅 የፈተና ቀን: ጳጉሜ 4 ቀን 2018 ዓ.ም

በዕለቱ በመረጣችሁት የፈተና ጣቢያ በአካል በመቅረብ ፈተናውን መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።

ጠቃሚ ማሳሰቢያዎችና የፈተና መመሪያዎች

✓ ተፈታኞች በእለቱ ከጠዋቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ በመፈተኛ ጣቢያዎች በአካል በመገኘት ሪፖርት ማድረግ ይጠበቅባቸባቸዋል።
✓ ፈተናው የሚሰጥባቸው የትምህርት አይነቶች ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያሉትን ባዮሎጂ፣ ኬሚስትሪ፣ ፊዚክስ፣ ሂሳብ እና እንግሊዝኛ ይሸፍናሉ።

✓ አመልካቾች ለፈተና ሲቀርቡ፦
o የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ውጤት
o የሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና አድሚሽን ካርድ (ወይም መታወቂያ)
o የምዝገባ ማረጋገጫ ኮፒ መያዝ ይኖርባቸዋል።


የተከለከሉ ነገሮች

✓በፈተናው ዕለት የሞባይል ስልኮችን እና ማንኛውንም ኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎችን ይዞ ወደ ፈተና ጣቢያ መግባት በጥብቅ የተከለከለ ነው።
• ዲሲፕሊን፡ በፈተና ወቅት ማንኛውንም ያልተገባ ተግባር መፈፀም በጥብቅ የተከለከለ ነው።


ልዩ ማስታወሻ፡ የመግቢያ ፈተናውን የሚያልፉ አመልካቾች በትምህርት ሚኒስቴር በኩል በሚደረገው መደበኛ የዩኒቨርሲቲ ምደባ ውስጥ አይካተቱም።
September 4, 2026 172