በአፋር ክልል ወረር ከተማ የሚገኘው መርከዝ ሰላም በትላንትናው ዕለት 36 የሚሆኑ የቁርአን ሂፍዝ ተማሪዎችን ለ6ኛ ጊዜ አስመርቋል። በዕለቱም የክልሉ የመጅሊስ አመራሮች ፣ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችና የሀገር ሽማግሌዎች ተገኝተዋል።
ቀደም ሲል ለመርከዙ ተማሪዎች በሐኒፍ ኢስላማዊ ድርጅት አዘጋጅነት ለ 4 ጊዜያት በተለያዩ የዒልም ዘርፎች ላይ አጫጭር ኮርሶች ሲሰጣቸው የቆየ ሲሆን። በዚሁ ልዩ አጋጣሚ ሐኒፍ ኢስላማዊ ድርጅት የተሰማውን ደስታ እየገለፀ ፤ ለተመራቂ ተማሪዎች ፣ ወላጆችና የመርከዙ አስተማሪዎች በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት ይወዳል።
ለዚህ ውጤት የለፉትን የመርከዙ ኃላፊዎችና አስተማሪዎችና አጋሮች በሙሉ አላህ ልፋታቸውን ይቀበላቸው በኸይርም ይመንዳቸው ፤ ተመራቂ ተማሪዎችንም ባወቁት የቁርአን ፋና ሰሪና ለሌሎችም አስተማሪ በመሆን ይህን ኸይር የሚያስቀጥሉ ያድርጋቸው።
Hanif Islamic Organization ∣ مؤسسة حنيف الإسلامية
@HanifMultimedia
7
5
2August 3, 2026 2.1K 2




