G-Tutorialclass: post #5238 — TG.ME

‎"እውነት ህግ ካለ ርሸና የፈጸሙና ያስፈፀሙ አካላት ሊጠየቁ ይገባል " - ነዋሪዎች

ከ13 ቀናት በፊት ‎በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ፦
° ተመስገን ጌታቸው
° ይታገሱ አሰግደው
° ግዛው ግርማዬ የተባሉ ሶስት ወጣቶች በትራንስፖርት እየተጓዙ በነበረበት ወቅት ከመኪና እንዲወርዱ ተደርገው መገደላቸው ይታወቃል።

ቃላቸውን ለቲክባህ የሰጡ የአከባቢው ኗሪዎች፤ "ሶስት ወጣቶች ከመኪና እንዲወርዱ ተደርገው እጃቸው የፊጢኝ ታስሮ በአሰቃቂ ሁኔታ ተረሽነው አስክሬናቸው በትውልድ አካባቢያቸው መገኘቱ እውነት ነው " ብለዋል።

የነዚህ ወጣቶች በፀጥታ ኃይሎች መገደልና ከግድያው በኋላ የሟቾቹ አስከሬን እንዳይነሳ ተብሎ በጅብ እንዲበላ መሆኑ በአካባቢው ማህበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ ቁጣ፣ ሀዘንና ስጋት መፍጠሩን ተናግረዋል።

" አስክሬናቸው ከሌሊቱ 11 ሰዓት አከባቢ በትውልድ ቀያቸው ተጥሎ ማንም እንዳያነሳና እንዳይቀብራቸው ማስጠንቀቂያ ከተሰጠ በኋላ አስክሬናቸው ለጅብ ተጋልጦ እንዲቆይ ሆኗል፤ ከሶስቱ የአንዱ ቤተሰቦቹ አንስተው ቀብረዋል " ሲሉ አብራርተዋል።

‎ነዋሪው " ‎'ፋኖ ናቸው' ተብለው ከመኪና እንዲወርዱ ከተደረጉ በኋላ በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸውን ነው የሰማነው። ይህ ‎በየትኛውም መመዘኛ ትክክል አይደለም፤ ጥፋትና ወንጀል ፈጽመው ከሆነ ወደ ፍርድ ቤት መውሰድ ይገባ ነበር። እውነትም ህግ ካለ በቁጥጥር ስር የዋሉ ሰዎችን የረሸኑ በህግ ሊጠየቁ ይገባል " ብለዋል።

ነዋሪዎች የተጎጂ ቤተሰቦች እየሆነ ያለውን ነገር ወጥተው ለመናገርና መረጃ ለመስጠት ይፈራሉም ተብሏል።
@Gtutorialclass
❤2
August 13, 2026 81 2