Event Addis Media: post #6975 — TG.ME

🔶አሻም ቲቪ በፍርድ ቤት ክርክር ተሸነፈ

አሻም ሚዲያ ትሬዲንግ የሰራተኞቹን የ4 ወር ያልተከፈለ ደሞዝ ሳይከፍል ተቋሙን መዝጋቱን ተከትሎ፣ የቀድሞ ሰራተኞቹ ባቀረቡት ክስ ፍርድ ቤት የሰራተኞቹን አሸናፊነት የሚገልፅ ውሳኔ አስተላልፏል።

​ሰራተኞቹ መብታቸውን ለማስከበር ላለፉት 6 ወራት በፍርድ ቤት በጽናት ሲከራከሩ የቆዩ ሲሆን፣ ፍርድ ቤት ባስተላለፈው ውሳኔ መሠረትም ተቋሙ ለሠራተኞቹ ያልከፈላቸውን ደሞዝ እና ተያያዥ ጥቅማጥቅሞች እንዲከፍል የሚያስገድድ ውሳኔ ወስኗል።

​ይህ ውሳኔ በሚዲያ ዘርፉ ውስጥ የሚሰሩ ባለሙያዎችን የሰራተኞችን መብትና ጥቅም ለማስከበር ትልቅ ማሳያ የሚሆን ሲሆን፣ ተቋማት የፋይናንስ ፈተና ቢገጥማቸው እንኳ የህግና የውል ግዴታቸውን መወጣት እንዳለባቸው ግልፅ መልእክት አስተላልፏል።

​ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤20👍7
August 17, 2026 2K 9